ጠ/ሚ ዐቢይ በህዳሴ ግድብ የመረጃ ልውውጥ ላይ ትኩረት ባደረገ ስብሰባ ላይ ተሳተፉ - መነሻ - am
嵌套Portlet
资源发布器
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
网页内容搜索
资源发布器
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መረጃ ልውውጥ ላይ ትኩረቱን ባደረገ ስብሰባ ላይ ተሳተፉ፡፡
በበይነ መረብ የተካሄደው ስብሰባ በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት እና የአፍሪካ ህብረት የወቅቱ ሊቀ መንበር ፌሊክስ ሺሴኬዲ የተዘጋጀ ሲሆን፥ በህዳሴ ግድብ ላይ መረጃ መለዋወጥን አላማው ያደረገ ነው፡፡
ሊቀ መንበሩ በዚህ ወቅት የአፍሪካ ጉዳዮች በህብረቱ ስር እንደሚቆዩ ጠቅሰው፥ ሁሉም አካላት በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር የሚያደርጉትን ድርድር መቀጠል ይገባቸዋል ብለዋል፡፡
በስብሰባው ላይ ፕሬዚዳንት ፊሊክስ ቲሼኬዲ ጉዳዩን አስመልክቶ በተገቢው ሰዓት ሙሉ ሪፖርቱን እንደሚያቀርቡ እና ውይይቱ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የአፍሪካ ጉዳይ በአፍሪካ ህብረት በኩል ሊፈታ እንደሚገባ ሊቀመንበሩ እንዳሰመሩበትም ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የትዊተር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ምንጭ፡- ኤፍ ቢ ሲ ፣ ሰኔ 17 ፣ 2013
嵌套Portlet
资源发布器
— 每页项目