በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ዘለቄታዊ ጠቀሜታ ላይ ያተኮረ ፎረም በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ተጀመረ - መነሻ - am
嵌套Portlet
资源发布器
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
网页内容搜索
资源发布器
በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዘለቄታዊ ጠቀሜታ ላይ ያተኮረ ሃገራዊ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል።
"የምሁራን ትብብርና ተሳትፎ ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዘለቄታዊ ጠቀሜታ" በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው ፎረም ላይ የሃገሪቱ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ምሁራንም እየተሣተፉ ነው።
በተጨማሪም በፎረሙ ላይ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሠር አፈወርቅ ካሱ ፣የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሣትፎ ማስተባበሪያ ምክርቤት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አረጋዊ በርሄን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ሃገራዊ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረሙ የሁለት ቀናት ቆይታ እንዳለውም መገለጹን ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ኤፍ.ቢ.ሲ
嵌套Portlet
资源发布器
— 每页项目