ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ድርድር ከመጭው ክረምት በፊት ይጠናቀቃል የሚል እምነት እንዳላት አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ - መነሻ - am
嵌套Portlet
资源发布器
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
网页内容搜索
资源发布器
ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ድርድር ከመጭው ክረምት በፊት ይጠናቀቃል የሚል እምነት እንዳላት አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ
አዲስ አበባ ፣ የካቲት 19 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ድርድር ከመጭው ክረምት በፊት ይጠናቀቃል የሚል እምነት እንዳላት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢኔ ኤሪክሰን ሶሬይድ ጋርተወያይተዋል፡፡
በዚህ ወቅትም በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ እና የታላቁ የህዳሴ ግድብ ድርድርን በተመለከተ ለሚኒስትሯ ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡
ከግድቡ ጋር በተያያዘ ያለውን ድርድርም ኢትዮጵያ ድርድሩን በቅንነት እያደረገች መሆኗን አስረድተዋል፡፡
አቶ ደመቀ በማብራሪያቸው በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ እየተካሄደ ያለው የሶስትዮሽ ድርድር ግድቡን ለመሙላት ከታሰበበት መጭው ክረምት በፊት ይጠናቀቃል የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡
嵌套Portlet
资源发布器
— 每页项目