የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህልውና ለመጠበቅ በተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ላይ ሁሉም አካል ርብርብ ሊያደርግ እንደሚገባ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሳሰቡ - መነሻ - am

嵌套Portlet

资源发布器

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ 星期五, 17 六月 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች 星期三, 8 六月 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ 星期三, 8 六月 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

资源发布器

የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህልውና ለመጠበቅ በተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ላይ ሁሉም አካል ርብርብ ሊያደርግ እንደሚገባ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሳሰቡ

ታህሳስ 25: 2013

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 25፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ህልውና ለመጠበቅ በተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ላይ ሁሉም አካል ርብርብ ሊያደርግ እንደሚገባ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አገኘሁ ተሻገር አሳሰቡ፡፡
የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የ2013 ዓ.ም የበጋ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ እንዲሁም ያለፉትን ዓመታት የሥራ ክንውን እውቅና የሚሰጥበት የንቅናቄ መድረክ በባሕር ዳር እያካሄደ ነው፡፡
በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አገኘሁ ተሻገር ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከመገንባት ባሻገር ለህልውናውም ማሰብ ተገቢ ነው ብለዋል፡፡
ግድቡ በደለል እዳይሞላ የተፈጥሩ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራን በጥራትና በስፋት ማካሄድ እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ አስገንዝበዋል፡፡
በእንቦጭ አረም ምክንያት አደጋ ላይ የወደቀዉን ጣና ሐይቅ ለመታደግ አረሙን ነቅሎ ማስወገድ ብቻ መፍትሄ ባለመሆኑ በደለል እንዳይሞላ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ በየአካባቢው ማከናወን ይገባል ብለዋል፡፡
የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኀላፊ ዶክተር መለሰ መኮንን በዘንድሮው የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ የሚሳተፉ አካላት ሥራዉ ዘላቂ እንዲሆን በባለቤትነት ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ መጠየቃቸውን አብመድ ዘግቧል።

嵌套Portlet

资源发布器