በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የተጀመረው ውይይት እንዲቀጥል ስምምነት ተደረሰ - መነሻ - am
嵌套Portlet
资源发布器
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
网页内容搜索
资源发布器
ቀነን፡ ታህሳስ 9 2013 ዓ.ም
በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የተጀመረው ውይይት እንዲቀጥል ስምምነት ተደረሰ
በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የተጀመረው የታላቁ የህዳሴ ግድብ የሦስትዮሽ ድርድር እንዲቀጥል ስምምነት ላይ መደረሱ ተገለጸ፡፡
የውሃ፣ የመስኖና ኢኒርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ከሱዳን የመስኖና የውሃ ሚኒስትር ፕሮፌሰር ያሲር አባስ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ሁለቱ ሚኒስትሮች በሦስትዮሹ የድርድር ሂደት ላይ መወያየታቸው የተጠቀሰ ሲሆን ድርድሩ እንዲቀጥል መወሰናቸው ነው የተሰማው፡፡
እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት የባለሙያዎች ቡድን በድርድሩ ሂደት ላይ ትልቅ ሚና እንዲኖረው ስምምነት ላይ መደረሱ ተገልጿል፡፡
የውሃ፣ የመስኖና ኢኒርጂ ሚኒስትር ዶክተር ስለሺ በቀለ ከሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ ጋርም ውይይት ማድረጋቸውን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኀን ዘግበዋል፡፡
(ኤፍ.ቢ.ሲ)
嵌套Portlet
资源发布器
— 每页项目