ዋሽንግተን የሚገኙ ታዳጊ ኢትዮጵያውያን ለህዳሴ ግድብ ገቢ አሰባሰቡ - መነሻ - am
嵌套Portlet
资源发布器
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
网页内容搜索
资源发布器
በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው የሚገኙ ታዳጊ ኢትዮጵያውያን የቡሄ በዓልን በማስመልከት በታዳጊ ሶፊ አስተባባሪነት ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አካሂደዋል፡፡
በፕሮግራሙ ላይም በቡሄ ጭፈራ የታጀቡ መልዕክቶችን ያስተላለፉ ሲሆን፣ ከነዚህ መልዕክቶች ውስጥ "የግድቡ መጠናቀቅ ህጻናትና ታዳጊዎች ትምህርታቸውን በአግባቡ በመከታተል የተሻለ ሕይወት እንዲመሩ ያስችላቸዋል" የሚለው ይገኝበታል፡፡
በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው መረጃውን ያጋሩት በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍፁም አረጋ የታዳጊ ሶፊ ብሎም የሁሉም ታዳጊዎች ሕልም እንዲሳካ ሁሉም ዜጎች ለግድቡ ግንባታ የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ በታዳጊዎቹ ስም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ዋልታ ነሃሴ 13/2013
嵌套Portlet
资源发布器
— 每页项目