የሕዳሴው ግድብ ሁለተኛ ዙር የውኃ ሙሌት በዓባይ የውኃ መጠን ላይ ተፅዕኖ አለመፍጠሩን ሱዳን ገለጸች - መነሻ - am

嵌套Portlet

资源发布器

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ 星期五, 17 六月 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች 星期三, 8 六月 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ 星期三, 8 六月 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

资源发布器

የሕዳሴው ግድብ ሁለተኛ ዙር የውኃ ሙሌት በዓባይ የውኃ መጠን ላይ ተፅዕኖ አለመፍጠሩን ሱዳን ገለጸች

የሕዳሴው ግድብ ሁለተኛ ዙር የውኃ ሙሌት ጋር ተያይዞ በዓባይ የውኃ መጠን ላይ ተፅዕኖ አለመፈጠሩን የሱዳኑ አል-ሩሳሬስ ግድብ ዋና ዳይሬክተር ሐሚድ ሞሐመድ ዓሊ አስታወቁ።
ሐሚድ ሞሐመድ ዓሊ እሁድ ዕለት በሰጡት መግለጫ፣ ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የውኃ ሙሌት ብትጀምርም በጥቁር ዓባይ የውኃ ፍሰት ላይ የጠብታ ያህል እንኳን ልዩነት አልታየም ብለዋል።
"በኢትዮጵያ አዋሳኝ ድንበር ላይ የሚገኘው አል-ዴይም ጣቢያ ከፈረንጆቹ ሚያዝያ ወር ጀምሮ ከኢትዮጵያ ወደ ሱዳን በሚፈስሰው የውኃ መጠን ላይ አንዲትም የጠብታ መቀነስ አዝማሚያ አላገኘም" ነው ያሉት።
የግድቡ ሁለተኛ የውኃ ሙሌት እየተከናወነ ቢሆንም በየዕለቱ ወደ ሱዳን የሚፈስሰው የውኃ መጠን አለመቀነሱን ነው የገለጹት።
ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ የሕዳሴውን ግድብ የውኃ ሙሌት ብታከናውንም የግድቡን የውኃ ሙሌት እና አሠራር በተመለከተ አሁንም ቢሆን ሕጋዊ እና አስገዳጅ ስምምነት መፈረም አለበት ሲሉ መናገራቸውን ሽንዋ ዘግቧል።

嵌套Portlet

资源发布器