የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ኢትዮጵያን በተለያዩ መስኮች ከፍ እንድትል ያደርጋል-ምሁራን - መነሻ - am

嵌套Portlet

资源发布器

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ 星期五, 17 六月 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች 星期三, 8 六月 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ 星期三, 8 六月 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

资源发布器

የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ኢትዮጵያን በተለያዩ መስኮች ከፍ እንድትል ያደርጋል-ምሁራን

የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ኢትዮጵያን በተለያዩ ዘርፎች ከፍ እንድትል የሚያስችላት መሆኑን የውሃ ጉዳይ ተመራማሪና የምጣኔ ሃብት ምሁራን ገለጹ፡፡

በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና አለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና የውሃ ጉዳዮች ተመራማሪው ዶክተር ውብእግዜር ፈረደ እንደሚሉት÷ የታላቁ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ወደ ስራ መግባት አዲስ የታሪክ ምዕራፍን የሚከፍት ነው፡፡

ኢትዮጵያ በቀጠናው ጂኦ-ፖለቲካ ያላትን ተደማጭነት በማሳደግ ረገድ ያለው ሚና ከፍ እንደሚልም ነው ተመራማሪው የጠቆሙት፡፡

ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የምጣኔ ሃብት ባለሙያ እንዲሁም የሶሾ-ኢኮኖሚ ጉዳዮች ተንታኙ አቶ ዋሲሁን በላይ በበኩላቸው÷ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ማነቆ ለሆነው የሃይል አቅርቦት ታላቁ የህዳሴ ግድብ ይዞት የሚመጣው ትሩፋት ከፍ ያለ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

በቂ የሆነ የሃይል አቅርቦትም አዳዲስ የቢዝነስ ዘርፎች እንዲተዋወቁ በማድረግ ረገድ የሚኖረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሚሆን አንስተዋል፡፡

የፕሮጀክቱ እውን መሆን ሌሎች አቅሞችን በማሳደግ ተጨማሪ ሃገራዊ ፕሮጀክቶችን እውን ለማድረግ እንደሚያግዝም ምሁራኑ አስረድተዋል፡፡

ታላቁ የህዳሴ ግድብን ለማጠናቀቅ ብሎም አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ለመገንባትም አንድነትን ማጠናከር እና የተጀመሩ የትብብር ስራዎችን ማነቃቃት እንደሚጠበቅ አሳስበዋል፡፡

ምንጭ፡- ኤፍ ሲ፣ ሰኔ 18 2013  

嵌套Portlet

资源发布器