የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ለህዳሴ ግድብ ግንባታ እስካሁን ከ205 ሚሊዮን ብር በላይ የቦንድ ግዥ መፈፀሙን አስታወቀ *********** - መነሻ - am
Nested Portlets
Asset Publisher
Statistics
Web Content Search
Asset Publisher
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ድረስ ከ205 ሚሊዮን ብር በላይ የቦንድ ግዥ መፈፀሙን አስታውቋል።
የህዳሴ ዋንጫውን ከኢፌዴሪ መከላከያ ተረከቦ ለሳምንታት የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ስራዎችን ሲሰራ የቆየው የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከያ ዘርፍ በዛሬው እለት የታላቁ ህዳሴ ዋንጫን ለወንጀል ምርመራ ዘርፍ በአዲስ አበባ ወዳጅነት አደባባይ አስረክቧል።
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከያ ዘርፍ ባለፉት ቀናት ለታላቁ ህዳሴ ግድብ 12 ሚሊዮን ብር ማሰባሰቡን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ ለ7 ዓመታት ባከናወናቸው ስራዎች ከ205 ሚሊዮን ብር በላይ የቦንድ ግዥ መፈፀሙንም ነው ያስታወቀው።
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከል ዘርፍ ምክትል ኮሚነር ጄኔራል መላኩ ፋንታ በዋንጫ ርክክብ ስነ-ስርዓቱ ወቅት ባስተላለፉት መልእክት ለዘመናት የህዝቦች ህልም የነበረውን ታላቁን ህዳሴ ግድብ እውን ሚሆንበት ጊዜ ላይ መሆናችን ወቅቱን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።
ፕሮጀክቱ የሁሉም ህብረተስብ አሻራ ያረፈበት ነው ያሉት ም/ል ኮሚሽነሩ ፕሮጀክቱን ከዳር ለማድረስም ሁሉም ኢትዮጵያውያን በላቀ ትብብር መስራት ይገባል ብለዋል፡፡
ፌዴራል ፖሊስ የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ ከተጣለበት ጊዜ አንስቶ ከማንኛውም ዓይነት ጥቃት ለመመከት አስተማማኝ ጥበቃ እያደረገና ህዝቡ የጣለበትን ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑንም ም/ል ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።
በሀገሪቱ በተለያዩ አከባቢዎች ያሚገኙ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን ደህንነት በመጠበቅ ረገድ የፌዴራል ፖሊስ ሀገራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ላይ ይገኛልም ነው ያሉት።
በመርሃ ግብሩ የኮሚሽኑ ከፍተኛ ኃላፊዎች እና ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ምንጭ፡- ኢቢሲ