ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 10,000 ብር በስጦታ ተበረከተ - መነሻ - am

Nested Portlets

Asset Publisher

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ Fri, 17 Jun 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች Wed, 8 Jun 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ Wed, 8 Jun 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Asset Publisher

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 10,000 ብር በስጦታ ተበረከተ

በውሃና ኢነርጂ ኤግዚቢሺን ላይ ሲታደሙ ያገኘናቸው አቶ ጌታቸው መንገሻ ለግድቡ ግንባታ የሚውል 10,000 ብር በስጦታ አበርክተዋል፡፡

አቶ ጌታቸው መንገሻ ነዋሪነታቸው በዩናይትድስቴት ኦፍአሜሪካ ሚኒሶታ ግዛት ሲሆን ውጭ ሀገር መኖር ከጀመሩ ከ20 ዓመታት በላይ ሆናቸዋል፡፡

ታዲያ ቤተዘመድ ለመጠየቅ ወደ ሀገር ቤት በቅርቡ እንደመጡ የሚናገሩት አቶ ጌታቸው መንገሻ የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ ኤግዚቢሺን በብሄራዊ ሳይንስ ሙዚየም ለእይታ ክፍት እንደሚሆን ሲሰሙ እጅግ መደሰታቸውን ገልጸዉልናል፡፡

አቶ ጌታቸው መንገሻ ሁሌም ስለሀገራቸው የሚያስቡ ከመሆናቸውም በለይ የህዳሴ ግድብ ተገንብቶ የሚጠናቀቅበት ጊዜ እንደናፈቃቸውና በጉግት እንደሚጠብቁት ተናግረው በግላቸው ማድረግ ሚገባቸውን ሁሉ ለማድረግ እንደሚሞክሩ ገልጸዋል፡፡

አምና ወደ ሀገር ቤት በመጡ ሰዓትም 10,000 ብር ለግድቡ ግንባታ የለገሱ ከመሆኑም በላይ ለመከላከያ ሰራዊት እንዲሁም በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ለተፈናቀሉ ዜጎች የበኩላቸውን ድርሻ ማበርከታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ታላቁ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን ከፍ ወዳለ ማማ የሚያደርስ ግድብ በመሆኑ ሌሎችም እንደዚሁ የየአቅማቸውን እየረዱ ሀገራችን በህዳሴ ግድብ ግንባታ እንዲሁም በሌሎች የልማት ዘርፎም ውጤታማ እንድትሆን መተባበር እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በአጠቃላይ በዘርፉ የተሰሩ ስራዎች እጅግ ተስፋ ሰጪና ኤግዚቢሺኑም ሳቢ በሆነ መልኩ የተሰዳ በመሆኑ ባዩት ነገር ስለመድሰታቸው ገለጽው የህዳሴ ግድብን እቦታው ድረስ ሄደው የመጎብኘት ዕቅድ እንዳላቸውም ተናግረዋል፡፡

Nested Portlets

Asset Publisher

— 5 Items per Page
Showing 1 - 5 of 16 results.