ግድቡ በመጭው ክረምት የቅድመ ምርት እንደሚጀምር ተገለጸ - መነሻ - am

Nested Portlets

Asset Publisher

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ Fri, 17 Jun 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች Wed, 8 Jun 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ Wed, 8 Jun 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Asset Publisher

ግድቡ በመጭው ክረምት የቅድመ ምርት እንደሚጀምር ተገለጸ
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በመጭው ክረምት የቅድመ ምርት እንደሚጀምር ተገለጸ፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከተለያዩ የሃይማኖት ተቋማትና ሲቪክ ማህበራት ጋር በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ተወያይቷል፡፡
በውይይቱ ላይ ግድቡ በክረምቱ የቅድመ ምርት እንደሚጀመር የተገለጸ ሲሆን፥ ለዚህ የሚያግዝ የ650 ኪሎ ሜትር መስመር ዝርጋታ ተከናውኗል ነው የተባለው፡፡
ከዚህ ባለፈም ግድቡ በመጭው ክረምት 18 ነጥብ 4 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ እንደሚይዝም በመድረኩ ተነስቷል፡፡
በውይይቱ ላይ የሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት ወቅቱን ጠብቆ እንደሚከናወንም ነው የተገለጸው፡፡
አሁን ላይ የግድቡ ግንባታ 80 በመቶ የደረሰ ሲሆን፥ የሲቪል ስራው 91 ነጥብ 8 በመቶ፣ የኤሌክትሮ መካኒካል 54 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሁም ሃይድሮሊክ ስትራክቸር 55 ነጥብ 2 በመቶ መድረሱ ተገልጿል፡፡
የግድቡ መጠናቀቅም የሃገሪቱን የኢነርጅ ሃይል በሰአት ከ73 ኪሎ ዋት ወደ 220 ኪሎ ዋት ያሸጋግረዋል ተብሏል፡፡
የግድቡን የሙሌት ሂደት ለማደናቀፍ የሚደረጉ ጥረቶችን፣ የኦፕሬሽን እና የውሃ አለቃቀቅ ሂደቶችን ኢትዮጵያ ፈጽሞ አትቀበልምም ነው የተባለው፡፡
የሃይማኖትና የሲቪክ ማህበራቱም ለግድቡ እውን መሆን እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡
በብስራት መለሰ
ኤፍ ቢ ሲ

Nested Portlets

Asset Publisher

— 5 Items per Page
Showing 1 - 5 of 16 results.