ኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ለሆነችው ኒጀር ገለፃ አደረገች - መነሻ - am

Nested Portlets

Asset Publisher

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ Fri, 17 Jun 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች Wed, 8 Jun 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ Wed, 8 Jun 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Asset Publisher

ኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ለሆነችው ኒጀር ገለፃ አደረገች

ኢትዮጵያ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በተመለከተ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ለሆነችው ኒጀር ማብራሪያ ሰጠች።

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ከኒጀሩ አቻቸው ሞሀመድ ባዞም ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።

መሪዎቹ ባደረጉት ውይይት የውሀ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በተመለከተ ኢትዮጵያ የያዘችውን እውነት አስረድተዋል።

ኒጀር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት የወቅቱ ተለዋጭ አባል ሀገራት መካከል አንዷ ናት።

የፀጥታው ምክር ቤት ከኢትዮጵያ ጋር በተገናኘ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን እና በትግራይ ክልል የተደረገውን የሕግ ማስከበር ዘመቻ በተመለከተ አሳስበውኛል የሚላቸውን ጉዳዮች ሲያነሳ እንደነበር ይታወቃል።

የፕሬዝዳንቷ የኒጀር ቆይታም ኒጀር ኢትዮጵያን በተመለከተ በፀጥታው ምክር ቤት በሚነሱ ጉዳዮች ላይ የተሻለ ግንዛቤ እንድትይዝ አድርጓታል ተብሏል።

በቅርቡ የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዶ/ር መሪየም አልሳዲቅ አልመህዲ ግድቡን በተመለከተ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ጋር መወያየታቸው ይታወሳል።

በተመሳሳይ ከዚህ ቀደም የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚንሰትር ሳሚ ሹክሪ የግድቡን ድርድር በተመለከተ የአገራቸውን አቋም ለማንጸባረቅ ወደ ተለያዩ የአፍሪካ አገራት ጉዞ አድርገው ነበር።

ኢትዮጵያም በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የያዘችውን እውነት እና አቋም ለማንፀባረቅ የምታደርገውን ጥረት አጠናክራ ቀጥላለች።(EBC)

Nested Portlets

Asset Publisher

— 5 Items per Page
Showing 1 - 5 of 16 results.