ኢትዮጵያ ሁለተኛው የግድቡ ሙሌት ከመጀመሩ በፊት መረጃዎችን ለመለዋወጥ ሱዳን እና ግብጽ ተወካይ እንዲሰይሙ ጋበዘች - መነሻ - am
Nested Portlets
Asset Publisher
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
Web Content Search
Asset Publisher
የውሃ፣ መስኖና ኢነርጅ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ሁለተኛው የግድቡ ሙሌት ከመጀመሩ በፊት መረጃዎችን ለመለዋወጥ ሱዳን እና ግብጽ ተወካይ እንዲሰይሙ ጋበዙ፡፡
ለሃገራቱ የውሃ ሚኒስትሮች በጻፉት ደብዳቤ በመጭው ክረምት ከሚጀመረው የግድቡ የውሃ ሙሌት ጋር በተያያዘ መረጃዎችን መለዋወጥ እንዲያስችል ሃገራቱ ተወካይ እንዲሰይሙ ጋብዘዋል፡፡
ሚኒስትሩ በደብዳቤያቸው ግብዣው ከሶስቱ ሃገራት በተውጣጣው ገለልተኛ የባለሙያዎች ቡድን በተዘጋጀው የግድቡ የውሃ ሙሌት የጊዜ ሰሌዳ ስምምነትን መሰረት ያደረገ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡
የግድቡ ግንባታ ሂደትና የክረምት ወቅት መቃረቡን ያነሱት ሚኒስትሩ በተግራባዊና አስፈላጊ ጉዳዮች ላይ በትብብር መስራት አስፈላጊ መሆኑን አስምረውበታል፡፡
የተወካዮች መሰየምም ትክክለኛ መረጃ ለመለዋወጥ ከማስቻሉም በላይ በአፍሪካ ህብረት አሸማጋይነት በሚካሄደው ድርድር ላይ መተማመንን ለመፍጠር እንደሚያግዝም ገልጸዋል፡፡
ኤፍ ቢ ሲ
Nested Portlets
Asset Publisher
መጣጥፎች
— 5 Items per Page