ኢትዮጵያ ከህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ የሚደረገውን ውይይት አጠናክራ ትቀጥላለች - ኢንጂነር ስለሽ በቀለ - መነሻ - am

Nested Portlets

Asset Publisher

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ Fri, 17 Jun 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች Wed, 8 Jun 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ Wed, 8 Jun 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Asset Publisher

ኢትዮጵያ ከህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ የሚደረገውን ውይይት አጠናክራ ትቀጥላለች - ኢንጂነር ስለሽ በቀለ

ኢትዮጵያ ከህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ የሚደረገውን ውይይት አጠናክራ ትቀጥላለች - ኢንጂነር ስለሽ በቀለ
አዲስ አበባ ፣ ጥር 27 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ የሚነሱ አለመግባባቶችን በውይይት ለመፍታት የምታደርገውን ጥረት እንደምትቀጥል የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ስለሺ በቀለ ገለጹ።
ዶክተር ስለሺ ከአልጀዚራ ዓረብኛ ቋንቋ ስርጭት ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በቆይታቸውም ኢትዮጵያ ግድቡን በተመለከተ የሚፈጠሩ አለመግባባቶች በውይይት መፈታት እንዳለባቸው ፅኑ አቋም ይዛለች ብለዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ግድቡን በተመለከተ መተማመን ያለበት ድርድር እንዲቀጥል ፍላጎቷ መሆኑን ጠቁመው፥ ከዚህ በተቃራኒው ግን በግድቡ ጉዳይ ላይ ውስብስብና አላስፈለጊ ጉዳዮች ተቀባይነት የላቸውም ብለዋል።
ከታችኛው የተፋሰሱ ሃገራት ጋር በተካሄደ ውይይት የቴክኒክ ጉዳዮችን በተመለከተ በበርካታ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መደረሱን ጠቁመዋል።
በግድቡ ላይ በአፍሪካ ህብረት አማካኝነት እየተካሄደ ያለውን የሶስትዮሽ ድርድር በተመለከተም ኢትዮጵያ በህብረቱ የሚካሄደው ድርድር እንዲቀጥል እየሰራች መሆኗን አስረድተዋል።
በዚህ ሂደት ግን ሱዳን ባለፉት ሰባት ወራት ውይይቱ ሰባት ጊዜ እንዲቋረጥ ማድረጓን አንስተዋል፤ ኢትዮጵያ በህብረቱ የሚካሄደውን ድርድር አስተጓጉላለች ተብሎ የሚወራው ወሬ ሃሰት መሆኑን በመጥቀስ።
ከዚህ ጋር ተያይዞም የኢትዮጵያን ቀጣይ የመልማት መብት የሚጻረር ማንኛውንም አይነት አንቀጽ በሕግና ደንብ ውስጥ ማካተት ተቀባይነት እንደማይኖረውም አስታውቀዋል።
ሚኒስትሩ ግድቡ በቀጠናው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚካሄድ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቅሰዋል።

Nested Portlets

Asset Publisher

— 5 Items per Page
Showing 1 - 5 of 16 results.