ኢትዮጵያ ከህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ የሚደረገውን ውይይት አጠናክራ ትቀጥላለች - ኢንጂነር ስለሽ በቀለ - መነሻ - am
Nested Portlets
Asset Publisher
Statistics
Web Content Search
Asset Publisher
ኢትዮጵያ ከህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ የሚደረገውን ውይይት አጠናክራ ትቀጥላለች - ኢንጂነር ስለሽ በቀለ
አዲስ አበባ ፣ ጥር 27 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ የሚነሱ አለመግባባቶችን በውይይት ለመፍታት የምታደርገውን ጥረት እንደምትቀጥል የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ስለሺ በቀለ ገለጹ።
ዶክተር ስለሺ ከአልጀዚራ ዓረብኛ ቋንቋ ስርጭት ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በቆይታቸውም ኢትዮጵያ ግድቡን በተመለከተ የሚፈጠሩ አለመግባባቶች በውይይት መፈታት እንዳለባቸው ፅኑ አቋም ይዛለች ብለዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ግድቡን በተመለከተ መተማመን ያለበት ድርድር እንዲቀጥል ፍላጎቷ መሆኑን ጠቁመው፥ ከዚህ በተቃራኒው ግን በግድቡ ጉዳይ ላይ ውስብስብና አላስፈለጊ ጉዳዮች ተቀባይነት የላቸውም ብለዋል።
ከታችኛው የተፋሰሱ ሃገራት ጋር በተካሄደ ውይይት የቴክኒክ ጉዳዮችን በተመለከተ በበርካታ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መደረሱን ጠቁመዋል።
በግድቡ ላይ በአፍሪካ ህብረት አማካኝነት እየተካሄደ ያለውን የሶስትዮሽ ድርድር በተመለከተም ኢትዮጵያ በህብረቱ የሚካሄደው ድርድር እንዲቀጥል እየሰራች መሆኗን አስረድተዋል።
በዚህ ሂደት ግን ሱዳን ባለፉት ሰባት ወራት ውይይቱ ሰባት ጊዜ እንዲቋረጥ ማድረጓን አንስተዋል፤ ኢትዮጵያ በህብረቱ የሚካሄደውን ድርድር አስተጓጉላለች ተብሎ የሚወራው ወሬ ሃሰት መሆኑን በመጥቀስ።
ከዚህ ጋር ተያይዞም የኢትዮጵያን ቀጣይ የመልማት መብት የሚጻረር ማንኛውንም አይነት አንቀጽ በሕግና ደንብ ውስጥ ማካተት ተቀባይነት እንደማይኖረውም አስታውቀዋል።
ሚኒስትሩ ግድቡ በቀጠናው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚካሄድ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቅሰዋል።