የህዳሴ ግድብን የተመለከተው የሶስትዮሽ ስብሰባ የአፍሪካ ህብረት በጨመራቸው ባለሙያዎች ሚና ላይ ተወያየ - መነሻ - am

Nested Portlets

Asset Publisher

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ Fri, 17 Jun 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች Wed, 8 Jun 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ Wed, 8 Jun 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Asset Publisher

የህዳሴ ግድብን የተመለከተው የሶስትዮሽ ስብሰባ የአፍሪካ ህብረት በጨመራቸው ባለሙያዎች ሚና ላይ ተወያየ
የህዳሴ ግድብን የተመለከተው የሶስትዮሽ ስብሰባ የአፍሪካ ህብረት በጨመራቸው ባለሙያዎች ሚና ላይ ውይይት አድርጓል።
የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር በበይነ መረብ በኢትዮጵያ ግብፅና ሱዳን የውሃ ሚኒስትሮች መካከል የተካሄደውን ውይይት አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል።
በመግለጫው ላይ የቀጣይ የድርድር ሂደትና የጊዜ ሰሌዳ የውይይቱ ዋነኛ አጀንዳ እንደነበር አስታውቋል።
በውይይቱ ከሶስቱም ሀገራት ሁለት ሁለት ባለሙያዎች በመመደብ በቀጣይ ህብረቱ በሰየማቸው ባለሙያዎች ተጨማሪ ሚና ዙሪያ ተወያይተው ለውሃ ሚኒስትሮች እንዲያቀርቡ ከስምምነት መደረሱን ጠቅሷል።
ባለሙያዎቹ ጥቅምት 23 ቀን 2013 ዓ.ም ተወያይተው ሪፖርታቸውን በማግስቱ ጥቅምት ለሚኒስትሮቹ ለማቅረብ ተስማምተዋልም ነው ያለው።
በዛሬው ስብሰባ የሰስቱ ሃገራት የህዳሴ ግድብን አስመልክቶ ጥቅምት 17 ቀን 2013 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ዓለም አቀፍ ግንኙነትና ትብብር ሚኒስትር እና በሶስቱ ሃገራት የውጭ እና የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ በተደረሰው የጋራ መግባባት መሰረት በድርድሩ ቀጣይ አካሄድና በጊዜ ሰሌዳው ዙሪያ ውይይት ተካሄዷል።
(ኤፍ ቢ ሲ)

Nested Portlets

Asset Publisher

— 5 Items per Page
Showing 1 - 5 of 16 results.