ሕዳሴ ግድብን ከደለል ለመታደግ የዓባይ ተፋሰስን በቆላ ቀርከሀ ለማልማት ስምምነት ተፈረመ - መነሻ - am
Nested Portlets
Asset Publisher
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
Web Content Search
Asset Publisher
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ከደለል ለመታደግ የዓባይ ተፋሰስን በቆላ ቀርከሀ ለማልማት ተቋማት ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱን የተፈራረሙት የአካባቢ ደን እና አየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽን፣ የአካባቢና ደን ምርምር ኢንስቲትዩት፣ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ እና ሰላሌ ዩኒቨርስቲ ናቸው፡፡
በመጀመሪያ ዙር በቆላ ቀርከሀ ለማልማት የታሰበው የደጀን እና የጎሀጽዮን የዓባይ ተፋሰስ ቆላማ አካባቢዎችን ነው ተብሏል፡፡
የአካባቢና ደን ምርምር ኢንስቲትዩትም የቆላ ቀርከሀ ዛፍ ችግኞችን እያባዛ መሆኑን ገልጿል፡፡
እስካሁን ድረስ 10 ሺህ ችግኞችን ማባዛቱን ኢንስቲትዩቱ ጠቅሶ በቀጣይም 500 ሺህ ለማባዛት ማቀዱን ጠቁሟል፡፡
የቆላ ቀርከሀ የዓባይ ተፋሰስ በደለል እንዳይሞላ እና ሥነ-ምኅዳሩ እንዲያገግም ከማድረግ ባለፈ ለአካባቢው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡
Nested Portlets
Asset Publisher
መጣጥፎች
— 5 Items per Page