የህዳሴ ግድብ ሱዳንን ከጎርፍ ጥፋት ይታደጋል—ኢንጂነር ስለሺ በቀለ - መነሻ - am

Nested Portlets

Asset Publisher

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ Fri, 17 Jun 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች Wed, 8 Jun 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ Wed, 8 Jun 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Asset Publisher

የህዳሴ ግድብ ሱዳንን ከጎርፍ ጥፋት ይታደጋል—ኢንጂነር ስለሺ በቀለ

የህዳሴ ግድብ ሱዳንን ከጎርፍ ጥፋት ይታደጋልኢንጂነር ስለሺ በቀለ
ሚኒስትሩ ትናንት በሰጡት መግለጫ በሱዳን በጎርፍ ምክኒያት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ሲያወድሙ በአስር ሽዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ደግሞ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል ብለዋል፡፡
በዘንድሮ አመት የህዳሴ ግድብ ውሃ ባይዝ ኖሮ ችግሩ የከፋ ይሆን እንደነበር ኢንጂነር ስለሺ ተናግረዋል።
እንደሚኒስትሩ ገለጻ ኢትዮጵያ በአባይ ላይ የምትገነባው የህዳሴ ግድብ በታችኞቹ የተፋሰስ ሃገራት የጎርፍ አደጋውን በመቀነስ ረገድ ትልቅ አስተዋጽዖ አበርክቷል።
የቀጠናው ሀገራት የጎርፍ መጥለቅለቅንና ድርቅን በማስተዳደርና ውሃ በማቅረብ ከሚገኙ ጥቅሞች በተጨማሪ የታዳሽ ኃይልን ለማዳበር የህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለውም አክለዋል፡፡
በመስከረም ወር አጋማሽ ላይ የሱዳን ሲቪል መከላከያ 121 ሰዎች በጎርፍ አደጋው መሞታቸውን አስታውቆ እንደነበር ይታወሳል።
ሲቪል መከላከያው በሀገሪቱ በርካታ ግዛቶች በሚገኙ የእርሻ መሬቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሰ አሎማህ ዶት ኮም (ALOMAH.COM) አመልክቷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር / አብይ አህመድ ባለፈው ወር ለተመድ ባደረጉት ንግግር «እኛ ሱዳንንም ሆነ ግብጽን የመጉዳት ፍላጎት የለንም» ይልቅስ ግድቡ በሁሉም ዘርፍ ለሁላችን ጠቃሚ ነው ማለታቸው ይታወሳል።
ግድቡ ለሶስቱ ሃገራት ግጭት ምንጭ ሊሆን እንደማይገባም ማስገንዘባቸው ይታወሳል።

ግድቡ ሲጠናቀቅ 65 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን የኤሌክትሪክ ኃይል ይሰጣል ፡፡

Nested Portlets

Asset Publisher

— 5 Items per Page
Showing 1 - 5 of 16 results.