የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ መሪዎች በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ - መነሻ - am

Nested Portlets

Asset Publisher

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ Fri, 17 Jun 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች Wed, 8 Jun 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ Wed, 8 Jun 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Asset Publisher

የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ መሪዎች በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ መሪዎች በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በዛሬው እለት ውይይት አካሂደዋል።

የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበርና የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ስሪል ራማፎሳ በቪዲዮ ኮንፈረንስ የተካሄደውን ስብሰባ መርተውታል።

በስብሰባው ላይም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ፣ የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ እና የግብፅ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ ተሳትፈዋል።

በተጨማሪም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋቂ መሃመትን ጨምሮ የቢሮው አባላት የሆኑት የኬንያ፣ የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና የማሊ ሀገራት መሪዎች እና ተወካዮችም ታድመዋል።

ውይይቱን ተከትሎም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ፥ በደቡብ አአፍሪካው ፕሬዚዳንት ስሪል ራማፎሳ አመቻችነት ለአፍሪካዊ ችግር አፍሪካዊ መፍትሄ የሚለውን ለማጠናከር ፍሬያማ ውይይት አካሂደናል ብለዋል።

በግድቡ ውሃ አሞላል ዙሪያም ቴክኒካዊ ውይይቶችን ቀጥሎ ለማካሄድ የጋራ መግባባት ላይ ለደረሱት የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ እና ለግብፅ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲም አድናቆታቸውን ገልፀዋል።

የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ መሪዎች ባሳለፍነው ሰኔ 19 ቀን 2012 ዓ.ም ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ ለታላቁ የሕዳሴ ግድብ ከአፍሪካ የመነጨ መፍትሔን ማበጀት ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል።

የዛሬው ውይይትም ባሳለፍነው ሰኔ 19 የተካሄደውን ውይይት ተከትሎ ነው የተካሄደው።

የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ መሪዎች እያካሄዱት ባለው ውይይት ላይም የሶስቱ ሀገራት ተደራዳሪዎች እስካሁን ባደረጉት ድርድር ዙሪያ ያቀረቡትን ሪፖርት ተመልክቷል።

ሪፖርቱን ተከትሎ በተደረገው ውይይትም ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ በህዳሴ ግድብ ውሃ አሞላል እና የስራ ክንውን ዙሪያ የቴክኒክ ድርድሮችን በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር ቀጥሎ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው ነው የተገለፀው።

Nested Portlets

Asset Publisher

— 5 Items per Page
Showing 1 - 5 of 16 results.