የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ለወጣቱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ተገለጸ - መነሻ - am

Nested Portlets

Asset Publisher

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ Fri, 17 Jun 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች Wed, 8 Jun 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ Wed, 8 Jun 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Asset Publisher

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ለወጣቱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ተገለጸ

በብሄራዊ ሳይንስ ሙዚየም ለዕይታ ክፍት የሆነው የውሃና ኢነርጂ ኤግዚቢሺን በርካቶች በግልም ሆነ በቡድን እየጎበኙት ይገኛሉ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልደታ ክፍለ ከተማ አስተባበሪነት በክፍለ ከተማው ከሚገኙ 10ም ወረዳዎች የተወጣጡ ከ300 በላይ ወጣቶች የውሃና ኢነርጂ ኤግዚቢሺንን በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል፡፡

ታዲያ በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 የወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆነውና በኤግዚቢሺኑ ጉብኝት ሲሳተፍ ያገኘነው ወጣት ያሬድ ግርማቸው ኤግዚቢሺኑ ለወጣቱ ስላለው ጠቀሜታና በግሉ ስላገኘው ግንዛቤ አብራርቷል፡፡

እንደ ወጣት ያሬድ ግርማቸው ገለጻ ወጣቶች በተለያዩ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ዘርፎች በንቃት በመሳተፍ ግንባር ቀደም ሚናቸዉን ሊጫወቱ ይገባል፡፡

በተለይ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለወጣቱ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ ለግድቡ ግንባታ መጠናቀቅ ወጣቶች በቀሪ ጊዜያት በንቅናቄ ስራዎች፣ ለግድቡ ግንባታ የሚውል የገንዘብ ልገሳ፣ የቦንድ ግዥ እንዲሁም በአከባቢ ጥበቃና ፐብሊክ ዲፕሎማሲ ተግባራት በንቃት መሳተፍ ይገባቸዋል ብሏል፡፡

Nested Portlets

Asset Publisher

— 5 Items per Page
Showing 1 - 5 of 16 results.