የተዝካር ወጪ ለህዳሴ ግድብ! - መነሻ - am
Nested Portlets
Asset Publisher
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
Web Content Search
Asset Publisher
በጀርመን ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ሌንሳ ተሾመ ከእናታቸው ሲስተር ፀሃይቱ ደስታ እና ሌሎች ልጆቻቸው ጋር በመመካከር ለአባታቸው አቶ ተሾመ ቦንጋሴ ወንታ 7ኛ ሙት ዓመት ተዝካር ወጪ ሊሆን የነበረ 100,000 ብር ለታላቁ ህዳሴ ግድብ አበርክተዋል።
ወይዘሮዋ ይህን ያደረጉት ከሁለት ልጆቻቸው ፊት ሲሆን ለዚህ ያነሳሳቸው ለሃገራቸው ያላቸው ፍቅር መሆኑን ተናግረው ሌሎችም ዜጎች በተመሳሳይ ለልደት፣ ለተዝካር እና ወዘተ ... የሚያወጡትን ወጪ ለግድቡ ቢያውሉ ትልቅ ማስታወሻ መሆኑን ተናግረዋል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አረጋዊ በርሄ ፤ የአቶ ተሾመ ቤተሰብ ያደረጉትን ድጋፍ በማመስገን ሁላችንም ኢትዮጵያውያን በዚህ መልኩ ታሪክ በመስራት የህዳሴ ግድባችንን አጠናቀን ሌሎች ግድቦችንም እንገነባለን ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
Nested Portlets
Asset Publisher
መጣጥፎች
— 5 Items per Page