በኒውዮርክ እና አካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለታላቁ የህዳሴ ግድብ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸው ተገለፀ፡፡ - መነሻ - am

Nested Portlets

Asset Publisher

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ Fri, 17 Jun 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች Wed, 8 Jun 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ Wed, 8 Jun 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Asset Publisher

በኒውዮርክ እና አካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለታላቁ የህዳሴ ግድብ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸው ተገለፀ፡፡

የገንዘብ ድጋፉ የተደረገው በትራይስቴት፣ በኒውዮርክ፣ በኒውጀርሲ፣ ኬነቲኬት እንዲሁም በሌሎች ስቴቶች ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በዌብናር በተደረገ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ፕሮግራም ላይ ነው፡፡

በውይይቱ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢ... ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ በክብር እንግድነት የተገኙ ሲሆን÷ የህዳሴው ግድብ ድርድር ሁለት ጊዜ በተ... የፀጥታው ምክርቤት የቀረበበት አግባብና ጉዳዩ በአፍሪካ መድረክ እንዲታይ የተደረገውን ብርቱ ትግልና ቀሪ ጉዳዮችን እንዲሁም እስካሁን የተመዘገበው ድል የሁሉም ጥረትና ተቀናጅቶ የመስራት ውጤት መሆኑን በንግግራቸው ጠቅሰዋል።

ኢንጂነር ጌዲዮን አስፋው በበኩላቸው÷ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የደረሰበትን ደረጃና የድርድሩ ሂደትን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ በተለይም በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የሚቀርቡትን የተሳሳቱ አመለካከቶች እና እንቅስቃሴዎች መመከት ያስፈልጋል ብለዋል።

አርቲስት ደበበ እሸቱ ሀገራችን ላይ በአሁኑ ጊዜ የሚታየው ችግር መነሻው ከአባይ ውሀ ጋር የተያያዘ ሲሆን÷ መፍትሄው ሁላችንም ከምንጊዜው በላይ ተደጋግፈን ልንቆም ይገባል ብለዋል።

ተሳታፊዎችም በቀረበላቸው ገለፃ÷ ደስተኛ መሆናቸውን በመግለጽ ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውል 62ሺህ ዶላር በላይ የገንዘብ ስጦታ ለግሰዋል።

ለወደፊቱም የታላቁን የህዳሴ ግድብ ግንባታ እስከሚጠናቀቅ የበኩላቸውን የፋይናንስ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ቃል መግታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት ያኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ኤፍ ነሃሴ 6 2013 .

Nested Portlets

Asset Publisher

— 5 Items per Page
Showing 1 - 5 of 16 results.