ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር በሙኒክ ተካሄደ። - መነሻ - am
Nested Portlets
Asset Publisher
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
Web Content Search
Asset Publisher
በጀርመን-ሙኒክ በኢትዮጵያ ማህበረሰብ አዘጋጅነት በተዘጋጀው በዚህ ፕሮግራም ላይ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል።
በተለያዩ ዘርፎች ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር”ደግሞ ለዓባይ!” በሚል መሪ ቃል ተካሂዷል።
በፕሮግራሙ ላይ ኢትዮጵያውያኑ እና ትውልደ ኢትዮጵያውያኑ ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ በቦንድ ግዥ፣ በመጽሔት ሽያጭና በስጦታ “ደግሞ ለዓባይ” በማለት በከፍተኛ ቁጭትና ፍላጎት የተሳተፉ ሲሆን በዚህም ከ15 ሺህ ዩሮ በላይ ገቢ ማሰባሰብ ተችሏል።
በጀርመን – ፍራንክፈርት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጄነራል ጽህፈት ቤት ቆንስል ጄኔራል አቶ ፈቃዱ በየነ በወቅቱ ባስተላለፉት መልእክት÷ በሚወዷት ሀገራቸው ሥም ተሰብስበው ሕዳሴ ግድቡን ለመደገፍ በመገኘታቸው ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል።
በጀርመን ሙኒክ አካባቢ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ በሁሉም ዘርፍ ሀገራቸውን ሲደግፉ የነበሩ መሆናቸውን በማውሳት÷ ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ቦንድ የተለመደ ድጋፋቸውን እንዲያደርጉና በቀጣይነት ይህንን ስብስብ ወደ መላው የኢትዮጵያ ቀን በማሳደግ በአንድነት ከሀገራቸው ጎን እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።
በጀርመን ሙኒክ አካባቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የቦንድ ግዢውን ሲፈጽሙ እንደተናገሩት÷ በዚህ ታሪካዊ ቀንም የዜግነታቸውን ድርሻ ለመወጣት ሀገራቸውን ለመደገፍ በመገኘታቸው የዜግነት ክብር እንደሚሰማቸው በመግለጽ በሁሉም ዘርፍ ድጋፋችንን አጠናክረን በማስቀጠል ለሀገራችን ያለንን ፍቅር በተግባር እንገልጻለን ማለታቸውንከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ኤፍ ቢ ሲ፣ ሐምሌ 19 ፣ 2013
Nested Portlets
Asset Publisher
መጣጥፎች
— 5 Items per Page