የህዳሴ ግድብ ድርድር የጋራ ተጠቃሚነትን ባከበረ መንገድ እንዲካሄድ የአሜሪካ “ብላክ ኮከስ” አባላት ጠየቁ - መነሻ - am

Nested Portlets

Asset Publisher

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ Fri, 17 Jun 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች Wed, 8 Jun 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ Wed, 8 Jun 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Asset Publisher

የህዳሴ ግድብ ድርድር የጋራ ተጠቃሚነትን ባከበረ መንገድ እንዲካሄድ የአሜሪካ “ብላክ ኮከስ” አባላት ጠየቁ

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት በማድረግ ድርድር እንዲካሄድ የአሜሪካ ኮንግረስብላክ ኮከስአባላት ጠየቁ።

በግድቡ ጉዳይ ላይ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ አሁንም የጋራ ተጠቃሚነትን እና ትብብር መሰረት ያረገ ሰላማዊ ድርድር ሊያደርጉ ይገባል ብሏል።

ይህ ድርድር የጋራ ተጠቃሚነትን እና ዓለም አቀፍ ህጎችን ያከበረ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት አባላቱ።

ግድቡ በአህጉሩ ትልቁ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ በመሆኑ ኤሌክትሪክ ለጎረቤት ሀጋራት በመላክ መልካም አጋጣሚ ሊሆን እንደሚችልም ጠቁመዋል።

ብላክ ኮከስአባላቱ አሜሪካ እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ተዋንያን በፈረንጆቹ 2015 ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ የፈረሙትን የሶስትዮሽ ድርድር ሊያከብሩ ይገባል ብለዋል።

አሜሪካ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት የህዳሴ ግድቡን በተመለከተ የአፍሪካ ህብረትን በማማከር ጠቃሚ ሚናውን እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል።

ሁሉም ወገኖች ተጠቃሚ የሚሆኑበት ሰላማዊ ድርድር እንዲካሄድ የአፍሪካ ህብረት ወሳኝ ሚና አለውም ነው ያሉት።

የአሜሪካ ኮንግረስብላክ ኮከስአባላት የህዳሴው ግድብ ለአህጉሪቱ ካለው ፋይዳ አንጻር እንዲጠናቀቅ ሰላማዊ ድርድርን እንደሚደግፉ አስታውቀዋል።

ኤፍ ሲ፣ ሰኔ 17 2013

Nested Portlets

Asset Publisher

— 5 Items per Page
Showing 1 - 5 of 16 results.