የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ መሪዎች በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ዛሬ ይመክራሉ - መነሻ - am
Nested Portlets
Asset Publisher
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
Web Content Search
Asset Publisher
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ መሪዎች በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ዛሬ ይመክራሉ።
የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ መሪዎች ባሳለፍነው ሰኔ 19 ቀን 2012 ዓ.ም ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ ለታላቁ የሕዳሴ ግድብ ከአፍሪካ የመነጨ መፍትሔን ማበጀት ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል።
የዛሬው ውይይትም ባሳለፍነው ሰኔ 19 የተካሄደውን ውይይት ተከትሎ የሚካሄድ መሆኑም ነው የተገለፀው።
የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበርና የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ስሪል ራማፎሳ በቪዲዮ ኮንፈረንስ የሚካሄደውን ስብሰባ ይመሩታልም ተብሎ ይጠበቃል።
በስብሰባው ላይ የቢሮው አባላት የሆኑት የኬንያ፣ የዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና የማሊ መሪዎች እና ተወካዮችም እንደሚሳተፉበት ይጠበቃል።
የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ በዛሬው ስብሰባውም ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ሲያደርጉት በነበሩት የሶስትዮሽ ድርድር የደረሱበትን ደረጃ የሚመለከት ይሆናል ተብሏል።
Nested Portlets
Asset Publisher
መጣጥፎች
— 5 Items per Page