ሕዳሴ ግድብን ከደለል ለመታደግ የዓባይ ተፋሰስን በቆላ ቀርከሀ ለማልማት ስምምነት ተፈረመ - መነሻ - am
Portlets aninhado
Publicador de Conteúdos e Mídias
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
Busca de Conteúdo Web
Publicador de Conteúdos e Mídias
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ከደለል ለመታደግ የዓባይ ተፋሰስን በቆላ ቀርከሀ ለማልማት ተቋማት ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱን የተፈራረሙት የአካባቢ ደን እና አየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽን፣ የአካባቢና ደን ምርምር ኢንስቲትዩት፣ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ እና ሰላሌ ዩኒቨርስቲ ናቸው፡፡
በመጀመሪያ ዙር በቆላ ቀርከሀ ለማልማት የታሰበው የደጀን እና የጎሀጽዮን የዓባይ ተፋሰስ ቆላማ አካባቢዎችን ነው ተብሏል፡፡
የአካባቢና ደን ምርምር ኢንስቲትዩትም የቆላ ቀርከሀ ዛፍ ችግኞችን እያባዛ መሆኑን ገልጿል፡፡
እስካሁን ድረስ 10 ሺህ ችግኞችን ማባዛቱን ኢንስቲትዩቱ ጠቅሶ በቀጣይም 500 ሺህ ለማባዛት ማቀዱን ጠቁሟል፡፡
የቆላ ቀርከሀ የዓባይ ተፋሰስ በደለል እንዳይሞላ እና ሥነ-ምኅዳሩ እንዲያገግም ከማድረግ ባለፈ ለአካባቢው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡
Portlets aninhado
Publicador de Conteúdos e Mídias
— 5 Itens por página