ጠ/ሚ ዐቢይ በህዳሴ ግድብ የመረጃ ልውውጥ ላይ ትኩረት ባደረገ ስብሰባ ላይ ተሳተፉ - መነሻ - am
ネスティッドポートレット
アセットパブリッシャー
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
Webコンテンツの検索
アセットパブリッシャー
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መረጃ ልውውጥ ላይ ትኩረቱን ባደረገ ስብሰባ ላይ ተሳተፉ፡፡
በበይነ መረብ የተካሄደው ስብሰባ በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት እና የአፍሪካ ህብረት የወቅቱ ሊቀ መንበር ፌሊክስ ሺሴኬዲ የተዘጋጀ ሲሆን፥ በህዳሴ ግድብ ላይ መረጃ መለዋወጥን አላማው ያደረገ ነው፡፡
ሊቀ መንበሩ በዚህ ወቅት የአፍሪካ ጉዳዮች በህብረቱ ስር እንደሚቆዩ ጠቅሰው፥ ሁሉም አካላት በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር የሚያደርጉትን ድርድር መቀጠል ይገባቸዋል ብለዋል፡፡
በስብሰባው ላይ ፕሬዚዳንት ፊሊክስ ቲሼኬዲ ጉዳዩን አስመልክቶ በተገቢው ሰዓት ሙሉ ሪፖርቱን እንደሚያቀርቡ እና ውይይቱ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የአፍሪካ ጉዳይ በአፍሪካ ህብረት በኩል ሊፈታ እንደሚገባ ሊቀመንበሩ እንዳሰመሩበትም ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የትዊተር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ምንጭ፡- ኤፍ ቢ ሲ ፣ ሰኔ 17 ፣ 2013
ネスティッドポートレット
アセットパブリッシャー
— ページごとの項目数 5