በሱዳንና በግብጽ ጥያቄ መሰረት ኢትዮጵያ እየገነባችው ባለው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ በሚቀጥለው ሳምንት ይሰበሰባል የተባለው የመንግሥታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት የጎላ ሚና እንደማይኖረው ተገለጸ። - መነሻ - am
ネスティッドポートレット
アセットパブリッシャー
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
Webコンテンツの検索
アセットパブリッシャー
በሱዳንና በግብጽ ጥያቄ መሰረት ኢትዮጵያ እየገነባችው ባለው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ በሚቀጥለው ሳምንት ይሰበሰባል የተባለው የመንግሥታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት የጎላ ሚና እንደማይኖረው ተገለጸ።
በሐምሌ ወር የምክር ቤቱ ሰብሳቢ የሆኑት በተባበሩት መንግሥታት የፈረንሳይ አምባሳደር የሆኑት ኒኮላስ ደ ሪቪዬር ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት የጸጥታው ምክር ቤት በሚቀጥለው ሳምንት በግድቡ ዙሪያ ውይይት ሊያደርግ ይችላል።
ነገር ግን ምክር ቤቱ ሦስቱን ሀገራት በመጥራት ስጋታቸውን እንዲገልጹና ከስምምነት ሊያደርሳቸው ወደሚችለው ድርድር እንዲመለሱ ከማበረታታት ውጪ ሊያደረግ የሚችለው ነገር እንደሌለ ገልጸዋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።
"ምክር ቤቱ ከዚያ የበለጠ ሊያደርግ የሚችለው ነገር አለ ብዬ አላስብም" ብለዋል ሰብሳቢው የፈረንሳይ አምባሳደር።
ምንጭ፡-ዋልታ፤ ሰኔ 25/2013
ネスティッドポートレット
アセットパブリッシャー
— ページごとの項目数 5