ትስስር ለሕዳሴ ግድብ ጥምረት ተመሰረተ - መነሻ - am
פורטלטים מקוננים
מוציא לאור של הנכס
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
חיפוש בתוכן אינטרנט
מוציא לאור של הנכס
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በቅንጅት የሚሰራ “ትስስር ለሕዳሴ ግድብ” የተሰኘ ጥምረት በይፋ ተመሰረተ።
ጥምረቱ ስለ ዓባይ ግድብ ያለውን እውነታ ለዓለም ማህበረሰብ ለማስረዳት የሚሰራ ሲሆን በሃገር ውስጥና በውጭ ያሉ ምሁራንና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሚናቸውን የሚወጡበት መሆኑን የህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አረጋዊ በርሄ ተናግረዋል።
የሙያ ማህበራት፣ የሃይማኖት ተቋማትና የፖለቲካ ፓርቲዎች አባሎቻቸውንና ተከታዮቻቸውን በማስተባበር ለሕዳሴ ግድቡ ድምጽ እንዲሆኑ አስተዋጽኦ ማበርከት የሚችሉበት እንደሆነም አክለዋል።
ኢትዮጵያውያንን በአንድ አጀንዳ የሚያሰባስበው ጥምረቱ ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ተጽዕኖ እንዲፈጥሩ የሚያስችላቸው መሆኑንም ገልጸዋል።
“አባቶች መስዋዕትነት ከፍለው ሃገሪቷን አስረክበውናል” ያሉት ዶክተር አረጋዊ፤ “እኛም ለቀጣዩ ትውልድ ግድቡን አጠናቀን በማስተላለፍ ታሪክ ማኖር አለብን” ብለዋል።
ጥምረቱ 12 አባላት ያሉት አስተባባሪ ኮሚቴ ያለው ሲሆን ሃብት አሰባሰብ፣ አካባቢ ጥበቃ፣ ህዝባዊ ዲፕሎማሲ እንዲሁም መገናኛ ብዙሃንና ተግባቦትን ያካተተ መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል።
ምንጭ፡- ኤፍ ቢ ሲ፤ ሰኔ 12 ፣ 2013
פורטלטים מקוננים
מוציא לאור של הנכס
— פריטים לדף