በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የተጀመረው ውይይት እንዲቀጥል ስምምነት ተደረሰ - መነሻ - am
Beágyazott portletek
Tartalom megjelenítő
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
Webtartalom-kereső
Tartalom megjelenítő
ቀነን፡ ታህሳስ 9 2013 ዓ.ም
በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የተጀመረው ውይይት እንዲቀጥል ስምምነት ተደረሰ
በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የተጀመረው የታላቁ የህዳሴ ግድብ የሦስትዮሽ ድርድር እንዲቀጥል ስምምነት ላይ መደረሱ ተገለጸ፡፡
የውሃ፣ የመስኖና ኢኒርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ከሱዳን የመስኖና የውሃ ሚኒስትር ፕሮፌሰር ያሲር አባስ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ሁለቱ ሚኒስትሮች በሦስትዮሹ የድርድር ሂደት ላይ መወያየታቸው የተጠቀሰ ሲሆን ድርድሩ እንዲቀጥል መወሰናቸው ነው የተሰማው፡፡
እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት የባለሙያዎች ቡድን በድርድሩ ሂደት ላይ ትልቅ ሚና እንዲኖረው ስምምነት ላይ መደረሱ ተገልጿል፡፡
የውሃ፣ የመስኖና ኢኒርጂ ሚኒስትር ዶክተር ስለሺ በቀለ ከሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ ጋርም ውይይት ማድረጋቸውን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኀን ዘግበዋል፡፡
(ኤፍ.ቢ.ሲ)
Beágyazott portletek
Tartalom megjelenítő
— Tételek oldalanként