ሕዳሴ ግድብን ከደለል ለመታደግ የዓባይ ተፋሰስን በቆላ ቀርከሀ ለማልማት ስምምነት ተፈረመ - መነሻ - am

Sisällytetyt portletit

Sisältöjulkaisija

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ pe, 17 kesäkuuta 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች ke, 8 kesäkuuta 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ ke, 8 kesäkuuta 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Sisältöjulkaisija

ሕዳሴ ግድብን ከደለል ለመታደግ የዓባይ ተፋሰስን በቆላ ቀርከሀ ለማልማት ስምምነት ተፈረመ

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ከደለል ለመታደግ የዓባይ ተፋሰስን በቆላ ቀርከሀ ለማልማት ተቋማት ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱን የተፈራረሙት የአካባቢ ደን እና አየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽን፣ የአካባቢና ደን ምርምር ኢንስቲትዩት፣ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ እና ሰላሌ ዩኒቨርስቲ ናቸው፡፡
በመጀመሪያ ዙር በቆላ ቀርከሀ ለማልማት የታሰበው የደጀን እና የጎሀጽዮን የዓባይ ተፋሰስ ቆላማ አካባቢዎችን ነው ተብሏል፡፡
የአካባቢና ደን ምርምር ኢንስቲትዩትም የቆላ ቀርከሀ ዛፍ ችግኞችን እያባዛ መሆኑን ገልጿል፡፡
እስካሁን ድረስ 10 ሺህ ችግኞችን ማባዛቱን ኢንስቲትዩቱ ጠቅሶ በቀጣይም 500 ሺህ ለማባዛት ማቀዱን ጠቁሟል፡፡
የቆላ ቀርከሀ የዓባይ ተፋሰስ በደለል እንዳይሞላ እና ሥነ-ምኅዳሩ እንዲያገግም ከማድረግ ባለፈ ለአካባቢው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡

Sisällytetyt portletit

Sisältöjulkaisija