የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ለታላቁ የሕዳሴ ግድብ ላበረከተው አስተዋጽኦ የእውቅና ሰርተፊኬት ተበረከተለት። - መነሻ - am

Sisällytetyt portletit

Sisältöjulkaisija

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ pe, 17 kesäkuuta 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች ke, 8 kesäkuuta 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ ke, 8 kesäkuuta 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Sisältöjulkaisija

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ለታላቁ የሕዳሴ ግድብ ላበረከተው አስተዋጽኦ የእውቅና ሰርተፊኬት ተበረከተለት።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ለታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ላደረገው አስተዋጽኦ ከሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የእውቅና ሰርተፊኬት ተሰጥቶታል። የእውቅና ሰርተፊኬቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አማካሪ ዶክተር ፎዚያ አሚን ተረክበዋል።
ሚኒስቴር መስሪያቤቱ እውቅና የተሰጠው ሠራተኞቹን በማስተባበር ካደረገው ድጋፍ ባሻገር በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ በማገዙና የማስተባበሪያ ጽ/ቤቱን ዌብ ሳይትና የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ላይ ባደረገው ከፍተኛ ተሳትፎ ነው።
ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሠራተኞች የብሔራዊ ዳታ ማዕከል አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ መሠረት ንጋቱ እና ወይዘሮ ብዙአየሁ ብርቄ በግል ላደረጉት ሙያዊ አስተዋጽኦ የእውቅናና የምስጋና ሰርቴፊኬት ተበርክቶላቸዋል።
በሚኒስትር ዲኤታ ማዕረግ የሚኒስትሩ አማካሪ ዶክተር ፎዚያ አሚን እንደተናገሩት ማስተባበሪያ ጽ/ቤቱ ለሰጠው እውቅና አመስግነው በቀጣይ ተቋሙ የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማገዝ ከጎናችሁ ይቆማል ብለዋል።
በግል እውቅና ያገኙትን ባለሙያዎች እገዛቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ያሉት ዶክተር ፎዚያ መሠል እውቅናዎች ሌሎችም ሠራተኞች ከተቋም ተልዕኮ በዘለለ አገራዊ ፕሮጀክቶችን በሙያቸው ለማገዝ የሚያደርጉትን ቁርጠኝነትና መነሳሳት ይጨምራል ብለዋል።

Sisällytetyt portletit

Sisältöjulkaisija