ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ድርድር ከመጭው ክረምት በፊት ይጠናቀቃል የሚል እምነት እንዳላት አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ - መነሻ - am
Portlets anidados
Publicador de contenidos
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
Búsqueda del contenido de Web
Publicador de contenidos
ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ድርድር ከመጭው ክረምት በፊት ይጠናቀቃል የሚል እምነት እንዳላት አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ
አዲስ አበባ ፣ የካቲት 19 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ድርድር ከመጭው ክረምት በፊት ይጠናቀቃል የሚል እምነት እንዳላት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢኔ ኤሪክሰን ሶሬይድ ጋርተወያይተዋል፡፡
በዚህ ወቅትም በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ እና የታላቁ የህዳሴ ግድብ ድርድርን በተመለከተ ለሚኒስትሯ ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡
ከግድቡ ጋር በተያያዘ ያለውን ድርድርም ኢትዮጵያ ድርድሩን በቅንነት እያደረገች መሆኗን አስረድተዋል፡፡
አቶ ደመቀ በማብራሪያቸው በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ እየተካሄደ ያለው የሶስትዮሽ ድርድር ግድቡን ለመሙላት ከታሰበበት መጭው ክረምት በፊት ይጠናቀቃል የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡
Portlets anidados
Publicador de contenidos
— Resultados por página