ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ - መነሻ - am
Portlets anidados
Publicador de contenidos
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
Búsqueda del contenido de Web
Publicador de contenidos
ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡
የአቀባበል ሥነ-ሥርዓቱ የአዳማ ከተማ ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት፣አባ ገዳዎች፣ ሃደ ስንቄዎች እንዲሁም የተለያዩ የማኀበረሰቡ ክፍሎች በተገኙበት በድምቀት ተካሂዷል።
በመክፈቻ መርሃ-ግብሩ ላይ የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኃይሉ ጀልዴ፥ ግድቡ የሀገራችን ሉዓላዊነትና የአንድነታችን ምልክት ነው ያሉ ሲሆን ግድቡ በዜጎች ተሳትፎ እንደተጀመረው ሁሉ በዜጎች ጉልበት፣ ሐብት እና አቅም በመጨረስ ለዓለም ተምሳሌት እንሆናለን ብለዋል።
የአዳማ ከተማ ነዋሪዎችና ባለሐብቶችም በከተማዋ የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን በግንባር ቀደምትነት በመሳተፍ ያሳዩትን ላቅ ያለ ተሳትፎ ለግድቡ መሳካትም በማበርከት የድርሻቸውን እንዲወጡ መልዕክት ማስተላለፋቸውንም ከከተማው ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ምንጭ፡- ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት
Portlets anidados
Publicador de contenidos
— Resultados por página