ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች - Welcome

Nested Portlets

Asset Publisher

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ Fri, 17 Jun 2022

ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገ Wed, 15 Jun 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች Wed, 8 Jun 2022

በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ለኅዳሴ ግድብ 42 ሚሊየን ብር ተሰበሰበ Wed, 8 Jun 2022

Facts about the Dam

× LOCATIONBenishangul-Gumuz region, Ethiopia.
× CONSTRUCTION STARTED:2011 G.C.
×Area: 1,874 sq KM
× RESERVOIR CAPACITY: 74 billion cubic metres

About GERD

Asset Publisher

Asset Publisher

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች
ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ገለጹ፡፡
በታንዛኒያ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ሽብሩ ማሞ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለታንዛኒያ ፕሬዝዳንት አቅርበዋል።
አምባሰደሩ የሹመት ደብዳቢቤያቸውን ባቀረቡበት ወቅት የሁለቱን ሀገራት የረጅም ዘመናት ግንኙነትና ቀጣይ የትብብር መስኮችን በሚመለከት ፕሬዝዳንቷ ጋር ሀሳብ ተለዋውጠዋል።
አምባሳደር ሽብሩ በኢትዮጵያ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ እና መንግሥት እየወሰዳቸው ስላለው እርምጃ እንዲሁም ስለ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ገለፃ ማድረጋቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡
በታንዛኒያ እስር ቤት በአስከፊ ችግር ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ተለቀው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱም ጥያቄ አቅርበዋል።
የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉሁ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ያጋጠማትን ችግር ለመፍታት መንግሥት እየወሰደ ያለውን እርምጃ እንደሚያደንቁ ተናግረዋል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታን በሚመለከትም ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት ነው ሲሉም ገልፀዋል።
በአዲስ አበባ የሚገኘውን የታንዛኒያ ኤምባሲ መሬት ጉዳይ በቅርቡ መፍትሔ እንዲያገኝ የኢትዮጵያ መንግሥት ያሳለፈው ውሳኔ እንዳስደሰታቸው የተናገሩት ፕሬዝዳንቷ የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ዘመን በማይሽረው ወዳጅነት የተሳሰረ በመሆኑ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በታንዛኒያ እስር ቤት ውስጥ የሚገኙ ዜጎች እንዲለቀቁና ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ለማድረግ መንግሥታቸው ቀና ውሳኔ እንደሚሰጥበትም አረጋግጠዋል።
ፕሬዝዳንት ሳሚያ የታንዛኒያ ዜጎች በኢትዮጵያ አቬሽን ዘርፍ ስልጠና እየወሰዱ መሆናቸውን አንስተው ለዚህም ኢትዮጵያ በዘርፉ ሙያ የአፍሪካ ተምሳሌት መሆኗን በመጥቀስ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ያላቸውን አድናቆት ገልፀዋል።
ዋልታ ፤ ሰኔ 1/2014

Asset Publisher

— 5 Items per Page
Showing 1 - 5 of 9 results.

About Us

Benefits of the Grand Renaissance Project

At the completion of the project, the average generation of 15,759 Giga watt hours per year will have a significant contribution to the national electricity system. The contribution of this project will be higher to reach the targets set by the rural electrification villages and to increase the supply from 44% to 90%.

The major components of the project

The Grand Ethiopian Renaissances Dam is being constructed for the purpose of generating electricity with total installed capacity of average annual energy production of about 15,759 GWh/yr.

Discharge rate about 1,547 m3/s.

The reservoir area will cover 1,874 square kilometers at full supply level of 640 meters above sea level maximum amd 590 metres minimum.

It has a 1.8 km length and 145 m height Roller Compacted Concrete dam.

Saddle Dam embankment of length 5.2 km and height 50 m.

The total storage volume is 74 billion cubic meters