ትስስር ለሕዳሴ ግድብ ጥምረት ተመሰረተ - መነሻ - am

Verschachtelte Portlets

Asset Publisher

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ Fr, 17 Jun 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች Mi, 8 Jun 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ Mi, 8 Jun 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Asset Publisher

ትስስር ለሕዳሴ ግድብ ጥምረት ተመሰረተ

ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በቅንጅት የሚሰራ “ትስስር ለሕዳሴ ግድብ” የተሰኘ ጥምረት በይፋ ተመሰረተ።

ጥምረቱ ስለ ዓባይ ግድብ ያለውን እውነታ ለዓለም ማህበረሰብ ለማስረዳት የሚሰራ ሲሆን በሃገር ውስጥና በውጭ ያሉ ምሁራንና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሚናቸውን የሚወጡበት መሆኑን የህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አረጋዊ በርሄ ተናግረዋል።
የሙያ ማህበራት፣ የሃይማኖት ተቋማትና የፖለቲካ ፓርቲዎች አባሎቻቸውንና ተከታዮቻቸውን በማስተባበር ለሕዳሴ ግድቡ ድምጽ እንዲሆኑ አስተዋጽኦ ማበርከት የሚችሉበት እንደሆነም አክለዋል።

ኢትዮጵያውያንን በአንድ አጀንዳ የሚያሰባስበው ጥምረቱ ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ተጽዕኖ እንዲፈጥሩ የሚያስችላቸው መሆኑንም ገልጸዋል።

አባቶች መስዋዕትነት ከፍለው ሃገሪቷን አስረክበውናልያሉት ዶክተር አረጋዊ፤እኛም ለቀጣዩ ትውልድ ግድቡን አጠናቀን በማስተላለፍ ታሪክ ማኖር አለብንብለዋል።

ጥምረቱ 12 አባላት ያሉት አስተባባሪ ኮሚቴ ያለው ሲሆን ሃብት አሰባሰብ፣ አካባቢ ጥበቃ፣ ህዝባዊ ዲፕሎማሲ እንዲሁም መገናኛ ብዙሃንና ተግባቦትን ያካተተ መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል።

ምንጭ፡- ኤፍ ሲ፤ ሰኔ 12 2013

Verschachtelte Portlets

Asset Publisher

— 5 Elemente pro Seite
Zeige 1 - 5 von 16 Ergebnissen.