የህዳሴ ግድብ በሱዳን ሲፈጠር የነበረን ጎርፍ በማስቀረት ተጨማሪ የእርሻ ቦታ እንደሚያስገኝላቸው የሱዳን አርሶ አደሮች ተናገሩ - መነሻ - am

Verschachtelte Portlets

Asset Publisher

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ Fr, 17 Jun 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች Mi, 8 Jun 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ Mi, 8 Jun 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Asset Publisher

የህዳሴ ግድብ በሱዳን ሲፈጠር የነበረን ጎርፍ በማስቀረት ተጨማሪ የእርሻ ቦታ እንደሚያስገኝላቸው የሱዳን አርሶ አደሮች ተናገሩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በሱዳን ሲፈጠር የነበረን የጎርፍ አደጋ በማስቀረት ተጨማሪ የእርሻ ቦታ እንዲያገኙ አድል እንደሚፈጥርላቸው የሱዳን አርሶ አደሮች ተናገሩ።

አልጀዚራ ያነጋገራቸው እነዚህ የሱዳን አርሶ አደሮች ግድቡ በግብፅ “ግሬት ዳም” አካባቢ የተስተካከለ የውሃ ፍሰት በመፍጠር ተጨማሪ የእርሻ ስፍራን እንደሚያጎናፅፋቸው ነው ከወዲሁ የተናገሩት።

የግብፅ “ግሬት ዳም” በሰሜናዊ ሱዳን ድንበር ላይ የሚገኝ ግድብ ነው።

የህዳሴ ግድብ መገንባት በየዓመቱ ጎርፍ በምርታቸው ላይ ያደርስ የነበረውን ጉዳት እንደሚቀንስ በመጠቆምም በግድቡ ላይ ያላቸውን ተስፋ ለአልጀዚራ ተናግረዋል።

በቀጣይ የወንዙ የውሃ ፍሰት የተስተካከለ እንደሚሆን በመግለፅም ከዚህ ቀደም በዓመት ሁለት ጊዜ ብቻ ያርሱ የነበረውን መሬት ሶስት ጊዜ ወደማረስ እንደሚሸጋገሩ ነው የጠቆሙት።

የሱዳን የውሃና መስኖ ሚኒስትሩ ያስር አባስ በበኩላቸው ኢትዮጵያ የህዳሴ ግደብ የውሃ ሙሌትን በያዝነው ወር ብትጀምር ሱዳን ተጠቃሚ እንደምትሆንም ነው ለአልጀዚራ አረብኛ የተናገሩት።

 462

 ShareFacebookTwitterTelegram

Verschachtelte Portlets

Asset Publisher

— 5 Elemente pro Seite
Zeige 1 - 5 von 16 Ergebnissen.