በሚኔሶታና ሚድዌስት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለህዳሴው ግድብ 40 ሺህ ዶላር አበረከቱ - መነሻ - am

Mòduls de portal imbricats

Editor de continguts

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ dv., 17 de juny 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች dc., 8 de juny 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ dc., 8 de juny 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Editor de continguts

በሚኔሶታና ሚድዌስት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለህዳሴው ግድብ 40 ሺህ ዶላር አበረከቱ

በሚኔሶታና ሚድዌስት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ያሰባሰበውን የ40 ሺህ ዶላር ድጋፍ አስረከበ፡፡

የኮሚቴው ሰብሳቢ ቄስ ፍራንሲስ ኮሚቴው በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ የሚነዙ የተሳሳቱ ትርክቶችን ለመመከትና ለግድቡ ግንባታ የሚሆን ሃብት ለማሰባሰብ መመስረቱን ገልጸዋል፡፡

ኮሚቴው ሁለተኛ 40 ሺህ ዶላር እያሰባሰበ መሆኑን ጠቅሰው፥ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሃብት ከማሰባሰብ ጎን ለጎን ከልዩ ልዩ አካላት ጋር በመተባባርና የአሜሪካ ምክር ቤት ተመራጮችን በማግባባት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስከብሩ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ስራዎችን እየሰራ ነው ብለዋል፡፡

በሚኔሶታ የኢፌዴሪ ቆንስል ጀነራል አምባሳደር አብዱላዚዝ መሐመድ በሚኔሶታና ሚድዌስት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለሃገራዊ ፕሮጀክቶችና ወቅታዊ ጥሪዎች ከፍተኛ ሃብት በማሰባሰብ የሃገር ባለውለታነታቸውን ማረጋገጣቸውን ጠቅሰዋል፡፡

በአካባቢው የሚኖሩ የዳያስፖራ ማህበረሰብ አባላት በዚህ ሳይወሰኑ በፐብሊክ ዲፕሎማሲና በሃገር ውስጥ የቀጥታ ኢንቨስትመንት እያሳዩት ያለው ተሳትፎም የሚበረታታ መሆኑን አንስተዋል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ዳያስፖራው እያደረገ ላለው አበረታች እንቅስቃሴ አመስግነው፥ ዳያስፖራው ከጊዜያዊ ልዩነት ይልቅ ለሃገራዊ አንድነት እንዲሰራ ጠይቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት በበኩላቸው ዳያስፖራው፥ በኮቪድ19 ምክንያት ችግር ውስጥ ሆኖ ሃገሩን ለማገዝ እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ማቅረባቸውን ከኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ዋና ዳይሬክተሯ አያይዘውም ወቅቱ ዳያስፖራው ከመቼውም ጊዜ በላይ አንድነቱን አጠናክሮ ለሃገሩ የሚቆምበት ወቅት መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

ኤፍ ቢ ሲ

Mòduls de portal imbricats

Editor de continguts

— 5 articles per pàgina
S'estan mostrant 1 - 5 de 16 resultats.