ግብጽ የግድቡ ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት የሚፈጥርባት ጫና እንደሌለ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ገለጹ - መነሻ - am

Mòduls de portal imbricats

Editor de continguts

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ባለፉት 11 ወራት ከ984 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ dv., 17 de juny 2022

ታንዛኒያ ሕዳሴ ግድቡ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገለጸች dc., 8 de juny 2022

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የዋንጫ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ተካሄደ፡፡ dc., 8 de juny 2022

Statistics

× አድራሻቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር

Editor de continguts

ግብጽ የግድቡ ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት የሚፈጥርባት ጫና እንደሌለ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ገለጹ

ታላቁ የኢትዮጵያ ግዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በግብጽ ላይ የሚፈጥረው ጫና እንደሌለ ካለም ያንን ለመቋቋመ የሚያስችል በቂ ውሃ እንዳላት የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚ ሽኩሪ ለአገሪቷ ፓርላማ አባላት ገለጸ።
ሑለተኛው ዙር የግድቡ ውሀ ሙሌት በግብጽ ላይ የሚያመጣው ጉዳት እንደሌለ ካለም ለመከላከል መንግስታቸው በቂ ዝግጅት ማድረጉን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ በአስዋን ግድብ በቂ ውሃ መያዛቸውን አብራርተዋል።
"የተደረጉ የቴክኒክ ጥናቶችን ተንተርሼ ነው" ገለጻውን የምሰጣችሁ ያሉት ሚኒስትሩ፤ በዘንድሮው የክረምት ወራት ከፍተኛ ጎርፍ ይጠበቃል፤ ስለሆነም ኢትዮጵያ ግድቧን ውሃ ብትሞላም የሚፈጠር ጫና የለም ከተፈጠረም ጎርፉ ግድባችንን መልሰን ለመሙላት ያግዘናል ብለዋል።
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግብጽ ላይ ጉዳት አያስከትልም። ነገር ግን ጉዳት የሚያመጣ ከሆነ በዚህ ረገድ እንደ አገር ያንን ለመቋቋም የሚያስችል በሁሉም መስክ አስፈላጊ ሀብት አለን ሲሉም ነው ሚኒስትሩ የገለጹት።
ኢትዮጵየ የግድቡ መገንባት በግብጽ ላይ የሚፈጥረው ጫና እንደሌለ በተደጋጋሚ ስትገልጽ ቆይታለች፤ የግድቡ ውሃ አሞላልም የታችኛውን የተፋሰሱ አገራት በማይጎዳ መልኩ እንደምታከናውን መግለጿ አይዘነጋም።
(ኢ ፕ ድ)

Mòduls de portal imbricats

Editor de continguts

— 5 articles per pàgina
S'estan mostrant 1 - 5 de 16 resultats.