የሕዳሴው ግድብ ሁለተኛ ዙር የውኃ ሙሌት በዓባይ የውኃ መጠን ላይ ተፅዕኖ አለመፍጠሩን ሱዳን ገለጸች - መነሻ - am
Mòduls de portal imbricats
Editor de continguts
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
Cerca de contingut web
Editor de continguts
የሕዳሴው ግድብ ሁለተኛ ዙር የውኃ ሙሌት ጋር ተያይዞ በዓባይ የውኃ መጠን ላይ ተፅዕኖ አለመፈጠሩን የሱዳኑ አል-ሩሳሬስ ግድብ ዋና ዳይሬክተር ሐሚድ ሞሐመድ ዓሊ አስታወቁ።
ሐሚድ ሞሐመድ ዓሊ እሁድ ዕለት በሰጡት መግለጫ፣ ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የውኃ ሙሌት ብትጀምርም በጥቁር ዓባይ የውኃ ፍሰት ላይ የጠብታ ያህል እንኳን ልዩነት አልታየም ብለዋል።
"በኢትዮጵያ አዋሳኝ ድንበር ላይ የሚገኘው አል-ዴይም ጣቢያ ከፈረንጆቹ ሚያዝያ ወር ጀምሮ ከኢትዮጵያ ወደ ሱዳን በሚፈስሰው የውኃ መጠን ላይ አንዲትም የጠብታ መቀነስ አዝማሚያ አላገኘም" ነው ያሉት።
የግድቡ ሁለተኛ የውኃ ሙሌት እየተከናወነ ቢሆንም በየዕለቱ ወደ ሱዳን የሚፈስሰው የውኃ መጠን አለመቀነሱን ነው የገለጹት።
ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ የሕዳሴውን ግድብ የውኃ ሙሌት ብታከናውንም የግድቡን የውኃ ሙሌት እና አሠራር በተመለከተ አሁንም ቢሆን ሕጋዊ እና አስገዳጅ ስምምነት መፈረም አለበት ሲሉ መናገራቸውን ሽንዋ ዘግቧል።
Mòduls de portal imbricats
Editor de continguts
— 5 articles per pàgina