ግድቡ የኢትዮጵያን የሀይል ችግር የሚፈታ፣ የሱዳንና የግብጽን ስጋት የሚቀንስ ነው -ጠ/ሚ ዐቢይ - መነሻ - am
Mòduls de portal imbricats
Editor de continguts
Statistics
× አድራሻ: ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ኢትዮጵያ.
× ግንባታዉ የተጀመረበት ጊዜ :2011 እ.ኤ.አ.
×ስፋት፡1,874 ስኩየር ኪሎ ሜትር
× የመያዝ አቅም: 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
Cerca de contingut web
Editor de continguts
በህዳሴ ግድብ ዙሪያ የምንከተለው ሂደት የኢትዮጵያን የሀይል ችግር የሚፈታ፣ የሱዳን እና የግብጽን ስጋት የሚቀንስ እንዲሁም በጋራ የምናድግበት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናገሩ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ እየሰጡ ነው፡፡
በምላሻቸው “በቀጠናው ሰላምና ብልጽግናን የሚያመጣ፣ ኃይል ሲመረት በጋራ የምንጠቀምበት፣ የውሃም ችግር ካለ እየተወያየን የምንፈታበት፣ ሰላማዊ የልማት ጉዞ እንዲሆን እንፈልጋለን፤ ለዚህም እየሰራን እንገኛለን” ብለዋል፡፡
ሃገራትም ኢትዮጵያ ሌሎችን የመጉዳት ፍላጎት ሳይሆን በትብብር የማደግ ፍላጎት እንዳላት ተገንዝበው ጉዳዩ ቶሎ ተቋጭቶ ወደ አዳዲስ ልማቶች ለመሄድ ማገዝ እንደሚገባቸውም አውስተዋል፡፡
በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩም ዛፍ በመትከልና ዝናብ በማብዛት የውሃ ብክነትን በመቀነስ ራስን በመጥቀም ሌሎችም እንዲጠቀሙ ይደረጋልም ነው ያሉት፡፡
ኤፍ ቢ ሲ፣ ሰኔ 28 ፣ 2013
Mòduls de portal imbricats
Editor de continguts
— 5 articles per pàgina